Search
Close this search box.

በሸደር የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ በፀሐይ የሚሠራ አነስተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ተመረቀ፡፡

በሸደር የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ በፀሐይ የሚሠራ አነስተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ተመረቀ፡፡

በሶማሌ ክልል ሸደር የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ተመርቆ የተከፈተው 254 ኪሎ ዋት ኃይል የሚያመነጨው ጣቢያ፣ 14 ሺህ ስደተኞች እና 3 ሺህ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተገልጿል፡፡

የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ወደ ሥራ መግባት፣ የስደተኞችና ተቀባይ ማህበረሰቡን ማህበረ-ኢኮኖሚያዊ ትስስር እንደሚያጠናክር ይታመናል፡፡

በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ የፌደራል ፔትሮሊየም እና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰህረላ አብዱላሂን ጨምሮ የሶማሌ ክልል ኃላፊዎች፣ የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ፕሮቴክሽን ዳይሬክተር አቶ ዳባ ለሜሳ፣ የለጋሽ ተቋማት ተወካዮች እና አጋሮች ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

Share: