በጋምቤላ የስደተኛችና ተመላሾች አገልግሎት የስደተኛ ህክምና ሪፈራል አሰጣጥ የዘጠኝ ወር አፈጻጸም በዛሬው እለት ተገመገመ፡፡ መስከረም 21/2016ዓ.ም
በዛሬው የግምገማ መድረክ የክልል ጤና ቢሮ፣የስደተኛ መጠለያ ጣቢያ ጤና ጣቢያዎች ፣አጎራባች ጤና ጣቢያዎች፣ሁለቱ የጋምቤላ ሆስፒታሎች፣ኩዋም፣አይ.አር.ሲ እና ሲቭ ዘ ችልድረን የተሳተፉበት ሲሆን በእለቱም የቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራሮች በተገኙበት ሰፊ ውይይት ተካሄድዋል፡፡
በቀጣይም ስራውን ለማቀላጠፍ ይረዳ ዘንድ ሁሉም አካልት መረባረብ እንዳለባቸው በመድረኩ ተነስቶአል በመጨረሻም ይህንን መድረክ በበጀት የደገፈውን ሴቭ ዘ ችልድረንን (SCI) በማመስደን ተጠናቁዋል፡፡