Gallery |Photos| Stories|

በጋምቤላ ክልል አልፎ አልፎ እየተፈጠሩ በማህበረሰቡ መካከል መቃቃር በመፍጠር ወደ ግጭት የሚያመሩ አለመግባባቶችን በዘላቂነት ለመፍታት ህዝባዊ የዕርቅ ጉባዔ ተካሄደ። ጉባዔው በክልሉ መንግሥት የተዘጋጀ ሲሆን፣ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎትን ጨምሮ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳትፈውበታል።