የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት አመራሩና ሠራተኛው በታደመበት በ2018 ዓ.ም የስድስት ወር ዕቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት አደረገ፡፡ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችም ውይይቱን በቨርቹዋል ተሳትፈዋል።
በዕቅድና ሪፖርት ዝግጅት ቡድን ዓበይት አፈጻጸሞችን፣ ያጋጠሙ ውስጣዊና ውጫዊ ተግዳሮቶችን፣ የተወሰዱ መፍትሄዎችንና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን የዳሰሰና ያመላከተ ተቋማዊ የአፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ፣ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎችና አስተያየቶች በሰፊው ተንሸራሽረዋል።
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ጠይባ ሐሰን ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፣ ቀጣይ የትኩረት አቅጫጫዎችንም አመላክተዋል፡፡
ኃብትን በአግባቡና በቁጠባ መጠቀም፣ ተጨማሪ ኃብት ማፈላለግ፣ ቁጠባን መሠረት ባደረገ መልኩ የአሠራር መመሪያዎችን መፈተሽ፣ ወዘተ ትኩረት እንደሚያሻቸው በውይይቱ ማጠቃለያ ገልጸዋል፡፡















